መልስ - ኢድ አልፈጥር እና ኢድ አል-አድሓ (አረፋ)
አነስ ባስተላለፈው ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ወደ መዲና በመጡ ጊዜ ሰዎቹ በደስታ የሚያሳልፏቸው ሁለት ቀናት ነበሯቸው። እርሳቸውም (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን)፡- "እነዚህ ሁለት ቀናት ምንድን ናቸው?" ብለው ጠየቁ፡ ሰዎቹም፡- "እኛ በቅድመ-ኢስላም የነበሩን የደስታ ቀናት ናቸው።" ብለው መለሱ። እርሳቸውም (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን)፦ "አላህ ከእነርሱ የተሻሉ በሆኑ ሁለት በዓላት ማለትም በዒድ አልፈጥር እና በዒድ አል-አድሓ ለውጦላችኋል።" አቡ ዳውድ ዘግበውታል።
ከእነዚህ ውጭ ያሉት በዓላት ቢድዓ ናቸው።