ጥ 5፡ አላህ ከዋለልህ ፀጋዎች የተወሰኑትን ጥቀስ?

መልስ-1- የእስልምና ፀጋ፤ ከከሃዲያን አለመሆንህ፤

2- የሱና ፀጋ፤ ከቢድዓ ሰዎች አለመሆንህ፤

3-የጤንነት ፀጋ፤ በመስማትም፣ በማየትም፣ በመራመድም በሌላውም ሁሉ ጤናማ መሆን፤

4- የመብላት፣ የመጠጣትና የመልበስ ፀጋ፤

ሌሎችም የዋለልን ስፍር ቁጥር የሌላቸው ፀጋዎችም ሁሉ።

የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {የአላህንም ጸጋ ብትቆጥሩ አትዘልቋትም። አላህ በእርግጥ መሓሪ አዛኝ ነውና።} [ሱረቱ-ነሕል፡18]