መልስ-
1- ግዴታ (ዋጂብ)፡- አምስቱ የግዴታ ሰላቶች፣ የረመዳን ፆም እና ወላጆችን ማክበርን ይመስል፤
ዋጂብ (ግዴታ) ማለት አድራጊው መልካም ምንዳ የሚያገኝበት ሲሆን የተወው ደግሞ ቅጣት ይጠብቀዋል።
2- ሙስተሐብ (የሚወደድ)፡- ከግዴታ ሶላት በኋላ የሚሰገዱ ሱናዎች፣ የሌሊት ሶላት፣ ሚስኪን ማብላት እና ሰላምታ መለዋወጥ መሰል ነገራቶችን ሲሆን አንዳንዴም "ሱና" ወይም "መንዱብ" ይባላል።
- ሙስተሓብ የሚባለው ቢሰሩት አጅር የሚያስገኝ ቢተውት የማያስቀጣ ነው።
ጠቃሚ (አንገብጋቢ) ማስታወሻ፡-
አንድ ሙስሊም የሆነ ጉዳይ ሱና ወይም ሙስተሐብ መሆኑን ሲሰማ ተግባራዊ ለማድረግና የነብዩን (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ፈለግ ለመከተል መጣደፍ ነው ይገባዋል።
3- ሙሐረም (የተከለከለ)፡- አልኮል መጠጣት፣ ወላጆችን ማመፅና ዝምድና መቁረጥን መሰል ተግባራቶችን ነው።
ሙሐረም የሆነ ነገር የተወ ሰው ምንዳ የሚያገኝበት የሰራ ደግሞ የሚቀጣበት ነው።
4- መኩሩህ (የተጠላ)፡- በግራ እጅ መስጠትና መቀበል፣ በሶላት ወቅት ልብስን (ክርን ላይ) መሰብሰብን ይመስል
- መክሩህ ነገርን መተው መልካም ምንዳን ያስገኛል፤ የሠራ ሰው ግን አይቀጣም።
5- ሙባሕ (የተፈቀደ)፡ ፖም እንደመብላትና ሻይ እንደመጠጣት አይነቱ ሲሆን "ሐላል" ወይ "ጃኢዝ" ይባላል።
- ሙባሕ ስላደረጉት ምናዳ አያሰጥም፤ ስላላደርጉት አያስቀጣም።