ጥ 27፡ በጉዞ ወቅት የሚባለውን ዱዓእን ጥቅስ?

መልስ- "አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ {ሱብሐነ አልለዚ ሰኸረ ለና ሀዛ ወማ ኩና ለሁ መቅሪኒን (13) ወኢና ኢላ ረቢና ለሙንቀሊቡን (14)} አልላሁመ ኢንና ነስአሉከ ፊ ሰፈሪና ሀዛ አል-ቢረ ወት-ተቅዋ ወሚነል ዐመሊ ማ ተርዷ አላሁመ ሀውዊን ዐለይና ሰፈሪና ሀዛ ወጥዊ ዓና ባዕደሁ አላሁመ አንታስ-ሷሒቡ ፊስ-ሰፈር ወል-ኸሊፈቱ ፊል-አህሊ አላሁመ ኢንኒ አዑዙ ቢከ ሚን ወዕሣኢ-ሰፈር ወካአባቲል-መንዞር ወሱኢል-ሙንቀለቢ ፊል-ማሊ ወል-አህል" (ትርጉሙም፡ አላህ ታላቅ ነው። አላህ ታላቅ ነው። አላህ ታላቅ ነው። «ያ ይህንን የማንችለው ስንሆን ለእኛ ያገራለን ጌታ ጥራት ይገባው። (13) እኛም በእርግጥ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን (14)» አላህ ሆይ! በዚህ ጉዟችን ለበጎነት እና ለመልካምነት አንተንም ለሚያስደስቱን ተግባሮች እንድትገጥመን እንማፀንሃለን። አላህ ሆይ! ይህን ጉዞ አቅልልን እና ርቀቱንም ቅርብ አድርግልን። አላህ ሆይ! በመንገዳችን ያለሀን ረዳታችን እና ለቤተሰቦቻችንም የተውንላቸው አንተን ነው። አላህ ሆይ! ከጉዞ መከራና ከክፉ እይታዎችም ባንተ እጠበቃለሁ። በቤተሰባችንና በንብረታችን ስንመለስ በችግር ውስጥ ከማግኘትም ባንተው እንጠበቃለን።)

ተመልሶም ሲመጣም እንዲሁ ካለ በኋላ ተከታዩንም ያክላል፦

"ኣይቡነ፤ ታኢቡነ፤ ዓቢዱን ሊረቢና ሐሚዱን" (ትርጉሙም፡ ጌታችንን እያመሰገንን ተፀፃቾችና፤ ተውባ አድራጊዎች፤ ለጌታችን አመስጋኞች ሆነን ተመለስን።) ሙስሊም ዘግበውታል።