መልስ - (በነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ላይ ሶለዋት አወርዳለሁ።) ሙስሊም ዘግበውታል። "አላሁምመ ረብበ ሐዚሂ አድዳዕወቲ አትታማህ፤ ወስ-ሶላቲ አል-ቃኢማህ፤ አቲ ሙሐመዲን አል-ወሲለተ ወልፈዲላህ፤ ወብዐሥሁ መቃመን መሕሙደን አልለዚ ወዐድተህ።" (ትርጉሙም፡ የዚህ የተሟላ ጥሪና የተቋቋመው ሶላት ጌታ አላህ ሆይ! (ነብዩ) ሙሐመድን "ወሲላ" እና "ፈዲላ" ለግሳቸው፤ ቃል በገባህላቸው በተከበረው ቦታም ቀስቅሳቸው።) ቡኻሪይ ዘግበውታል።
በአዛንና በኢቃማ መካከልም ዱዓ ታደርጋለህ፤ ምክንያቱም በዛ ሰአት የተደረገ ዱዓእ አይመለስምና።