መልስ-
1- የላቀው አላህ መብቶችን የመጠበቅ አደራ፤
መገለጫዎቹ፡- እንደ ሶላት፣ ዘካ፣ ጾም፣ ሐጅ እና ሌሎችንም አላህ በኛው ላይ ግዴታ ያደረጋቸውን ዒባዳዎች የመተግበር አማና፤
2 - የፍጥረታትን ሐቆች የመጠበቅ አማና:
· የሰዎችን ክብር
· ገንዘባቸውንም
· ህይወታቸውንም በመጠበቅ
· እንዲሁም ምስጢራቸውንና ሰዎች በአደራ መልኩ የሰጡት ሁሉ በዚሁ የሚጠቃለል ነው።
የላቀው አላህ ስለሚድኑት ሰዎች ባህርያት ሲገልፅ እንዲህ ብሏል:- {እነዚያም እነርሱ ለአደራዎቻቸውና ለቃል ኪዳናቸው ጠባቂዎች። 8} [ሱረቱል ሙሚኑን፡ 8]