መልስ-1- የተመሰገነ ቁጣ፡- ይሀውም ከሓዲዎች፣ ሙናፊቆችም ሆኑ ሌሎች የአላህን ድንበር ሲጥሱ ለአላህ ተብሎ የሚደረግ ቁጣ ነው።
2- የተወገዘ ቁጣ፡- ይኸውም አንድ ሰው ማድረግ የማይገባውን እንዲያደርግና እንዲናገር የሚያደርገው የቁጣ ዓይነት ነው።
ለተወገዘው የቁጣ ዓይነት መፍትሄው፦
ውዱእ ማድረግ፤
ቆሞ ከነበረ መቀመጥ፤ ተቀምጦ ከነበረ ደግሞ መጋደም፤
በዚህ ረገድ ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ያስተላለፉትን ትእዛዝ መተግበር፡- “አትቆጣ!"
በተናደደ ጊዜ በስሜታዊነት ሌላ ነገር ውስጥ እንዳይገባ ራስን መቆጣጠር፤
"አዑዙ ቢላህ" ብሎ ከተረገመው ሰይጣን ተንኮል በአላህ መጠበቅ፤
ዝምታ።