መልስ- መልካም ነገርን ወይም ደግሞ ማድረግ የሚጠበቅበትን ነገር ከማድረግ መስነፍ ነው።
ግዴታ ነገራቶችን ከማድረግ መሰላቸትን እንደምሳሌ መጥቀስ ይቻላል።
የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ {መናፍቃን አላህን ያታልላሉ። እርሱም አታላያቸው ነው። (ይቀጣቸዋል)። ወደ ሶላትም በቆሙ ጊዜ ታካቾች ስዎችን የሚያሳዩ ሆነው ይቆማሉ። አላህንም ጥቂትን እንጅ አያወሱም። 142} [ሱረቱ-ኒሳእ፡ 142]
በመሆኑም ሙእሚን ስልቹነትን፣ መኮፈስንና ስንፍናን ትቶ በዱኒያዊ ጉዳዩም ቢሆን አላህን በሚያስደስት ሥራና እንቅስቃሴ በትጋትና በጥረት ሊጣደፍ ይገባዋል።