መልስ-1- በእውነት ላይ መኩራራት፡ እውነትን መገፍተርና አለመቀበል ነው።
2- በሰዎች ላይ መኩራራት፡ ሰዎችን ማቃለልና ማንቋሸሽ ነው።
የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "በልቡ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያክል ኩራት ያለበት ጀነት አይገባም።" አስከትሎ አንድ ሰው፡- "የሆነ ሰው ልብሱም ጥሩ፣ ጫማውም ጥሩ እንዲሆን ቢወድስ? ሲል እርሳቸውም፦ "አላህ ውብ ነው፤ ውብ ነገርንም ይወዳል። ኩራት ማለት እውነታን መገፍተርና ሰዎችን መናቅ ነው።" ሙስሊም ዘግበውታል።
- እውነታን መገፍተር ማለት እውነትን አለመቀበል ማለት ነው።
- ሰዎችን መናቅ ሲባል ደግሞ ሰዎችን አሳንሶ ማየት ነው።
- ጥሩ ቀሚስ እና ጥሩ ጫማ መልበሱ ኩራት አይደለም።