መልስ-1- ህመም ከተሰማኝ ቀኝ እጄን በሚያመኝ ስፍራ ላይ አድርጌ ሶስት ጊዜ "ቢስሚላህ" ካልኩ በኋላ ሰባት ጊዜ እንዲህ እላለሁ "አዑዙ ቢዒዘቲላሂ ወቁድረቲሂ ሚን ሸሪ ማ አጂዱ ወኡሓዚሩ" (ትርጉሙም: ከማገኘው ክፋት በአላህ ክብር እና ሀይል እጠበቃለሁ እና እጠነቀቃለሁ።"
2- አላህ በወሰነው ነገር ወድጄ እታገሳለሁ፤
3- የታመመ ወንድሜን ለመጠየቅ እሯሯጣለሁ ዱዓእም አደርግለታለሁ፤ እርሱ ዘንድ ግን አብዝቼ አልቀመጥም።
4- ገና ሳይጠይቀኝ ሩቃ አደርግለታለሁ፤
5- በሚችለው መጠን እንዲታገስ፣ ዱዓእ እንዲያደርግ፣ ሶላቱንም እንዲሰግድና በቻለው ልክ ንፅህናውንም እንዲጠብቅ እመክረዋለሁ፤
6- ለህመምተኛ የሚደረገው ዱዓእ ሰባት ጊዜ እንዲህ ማለት ነው፡- "አስአሉ አላሀ አልዐዚም ረበ አልዐርሺል አልዐዚም አን የሽፊየከ" (ትርጉሙም: ታላቅ የሆነውን እና የዐርሽ ጌታ የሆነውን አላህ እንዲያሽርህ እለምነዋለሁ።"