መልስ - 1 - አላህን በማመፅ ላይ እስካልሆነ ድረስ ወላጆችን መታዘዝ፤
2- ወላጆችን መኸደም (መንከባከብ)፤
3 - ወላጆችን ማገዝ፤
4- የወላጆችን ጉዳይ ማሳካት፤
5- ለወላጆች ዱዓእ ማድረግ፤
6- ከእነርሱ ጋር ሲጫወቱ ስርአትን መጠበቅ ይገባል፤ በዚህም መሰረት ከንግግሮች ትንሽ የሆነው “ኡፍ” ማለት እንኳ አይፈቀድም።
7- ለወላጆች የፈገግታ ፊትን ማሳየት ለነርሱ ፊትን አለማጨፍገግ፤
8 - ድምፄን ከወላጆቼ ድምጽ በላይ ከፍ አላደርግም፤ በጥሞና አዳምጣቸዋለሁኝም፤ በንግግራቸው መሀል አላቋረጣቸውምም፤ በስማቸው ነጥየም አልጠራቸውም፤ ይልቁን “አባየ!” “እማየ!” ነው የምላቸው።
9- አባትና እናቴ ክፍል ውስጥ እያሉ ከመግባቴ በፊት ፈቃዳቸውን እጠይቃለሁ፤
10- የወላጆቻችንን እጆችና ግንባራቸውን መሳም።