መልስ-1- ወደ ቦታው ከመግባቴ በፊት ፈቃድ እጠይቃለሁ:
2- ፍቃድ የምጠይቀው ሶስት ጊዜ ሲሆን ከዚያ በላይ ከቆዩብኝ ትቼ እሄዳለሁ፤
3- በር ሳንኳኳ በቀስታ ነው፤ አንኳኩቼ ስቆምም በበሩ ፊት ለፊት ሳይሆን ወደ ቀኝ ወይም ወደ ግራ ዞር ብዬ ነው የምቆመው፤
4- ወደ አባቴ ወይም ወደ እናቴ አልያም ወደ ማንኛውም ሰው ክፍል ውስጥ ፍቃዳቸውን ሳልጠይቅ አልገባም፤ በተለይም ጊዜው ጎህ ከመቅደዱ በፊት፣ እኩለ ቀን ላይ ከዝሁር ሶላት በፊት (አረፍ በሚሉበት ሰአት) እና ከዒሻ ሶላት በኋላ ከሆነ፤
5- ሰው መኖርያው አድርጎ ያልያዛቸው ቦታዎች ለምሳሌ፡ ሆስፒታል ወይም ሱቅ ከሆነ ግን ፍቃድ ሳልጠይቅም መግባት እችላለሁ፤