መልስ-1- ስገባ ቀኝ እግሬን አስቀድሜ እገባለሁ፤
2- ከመግባቴ በፊትም እንዲህ እላለሁ፡- "ቢስሚላሂ አልላሁማ ኢኒ አዑዙ ቢከ ሚነል-ኩብሢ ወልኸባኢሥ" (ትርጉሙም፡ በአላህ ስም አላህ ሆይ! ከክፉ ወንድም ሆነ ሴት ጂን በአንተ እጠበቃለሁ።)
3- የአላህ ስም የተጠቀሰበትን ነገር ይዤ አልገባም፤
4 - ስፀዳዳም እደበቃለሁ፤
5- በምፀዳዳበት ጊዜ አላወራም፤
6- ሽንትም ይሁን ሰገራ ስፀዳዳ ወደ ቂብላም አልዞርም ጀርባየንም ለቂብላ አልሰጥም፤
7- ነጃሳን ለማስወገድ ግራ እጄን እጠቀማለሁ እንጂ ቀኝ እጄን አልጠቀምም፤
8- ሰዎች በሚጓዙበት መንገድ ወይም ጥላ ስር አልፀዳዳም፤
9- ከተፀዳዳሁ በኋላ እጄን እታጥባለሁ፤
10 - ግራ እግሬን አስቀድሜ እወጣለሁ “ጉፍራነክ” እላለሁ፤