ጥ 17፡ የመፀዳዳት ሥነ-ስርአትን (አዳብ) ይጥቀሱ?

መልስ-1- ስገባ ቀኝ እግሬን አስቀድሜ እገባለሁ፤

2- ከመግባቴ በፊትም እንዲህ እላለሁ፡- "ቢስሚላሂ አልላሁማ ኢኒ አዑዙ ቢከ ሚነል-ኩብሢ ወልኸባኢሥ" (ትርጉሙም፡ በአላህ ስም አላህ ሆይ! ከክፉ ወንድም ሆነ ሴት ጂን በአንተ እጠበቃለሁ።)

3- የአላህ ስም የተጠቀሰበትን ነገር ይዤ አልገባም፤

4 - ስፀዳዳም እደበቃለሁ፤

5- በምፀዳዳበት ጊዜ አላወራም፤

6- ሽንትም ይሁን ሰገራ ስፀዳዳ ወደ ቂብላም አልዞርም ጀርባየንም ለቂብላ አልሰጥም፤

7- ነጃሳን ለማስወገድ ግራ እጄን እጠቀማለሁ እንጂ ቀኝ እጄን አልጠቀምም፤

8- ሰዎች በሚጓዙበት መንገድ ወይም ጥላ ስር አልፀዳዳም፤

9- ከተፀዳዳሁ በኋላ እጄን እታጥባለሁ፤

10 - ግራ እግሬን አስቀድሜ እወጣለሁ “ጉፍራነክ” እላለሁ፤