ጥ13፡ የአለባበስ ሥነ-ስርአትን (አዳብ) ዘርዝር?

መልስ - 1 - ልብሴን በቀኝ በኩል ጀምሬ እየለበስኩ አላህን አመሰግነዋለሁ፤

2- ልብሴን ከቁርጭምጭሚቴ ወደታች አላረዝምም፤

3- ወንድ ልጆች የሴቶችን ልብስ ሴት ልጆችም የወንዶችን ልብስ አይለብሱም፤

4- ልብሴ የከሀዲዎችንና የኃጢአተኞችን ልብስ አለመምሰል ይጠበቅበታል፤

5- ልብስ በሚይወልቁበት ጊዜ "ቢስሚላህ" ማለት፤

6- ጫማ ሲደረግም መጀመሪያ ላይ በቀኝ በኩል ሲወለቅ ደግሞ በግራ በኩል ነው።