መልስ-
1 - በመብላትና በመጠጣቴ ልዕለ ኃያል የሆነው አላህን መታዘዝን ነው የማስበው፤
2- ከመመገቤ በፊት እጄን እታጠባለሁ፤
3- "ቢስሚላህ" ብየ ከመአዱ መሀልም ከሌላ ሰው ፊትም ሳይሆን በፊትለፊቴ ካለው በቀኝ እጄ እበላለሁ፤
4- "ቢስሚላህ" ማለትን ከረሳሁ ባስታወስኩበት ጊዜ እንዲህ እላለሁ "ቢስሚላሂ አወሊሂ ወአኺሪሂ"
5- ከምግቡ የተገኘውን እመገባለሁ፤ ምግቡንም አላነውርም፤ ከወደድኩት እበላዋለሁ ባልወደ እንኳ አላነውረውም፤
6- ጥቂት ጉርሻዎችን እበላለሁ እንጂ አብዝቼ አልመገብም፤
7- ምግብና መጠጥ ላይ አልተነፍስም፤ እስኪቀዘቅዝ ድረስ ማቆየት ካለብኝ አቆየዋለሁ እንጂ፤
8- ማእዱን ከቤተሰብና ከእንግዳ ጋር እጋራለሁ፤
9- ከእኔ ከሚበልጠኝ ሰው ጋር ስቀርብ ቀድሜው መብላት አልጀምርም፤
10- ስጠጣም "ቢስሚላህ" ብየ ተቀምጬ ሦስት ጊዜ ተጎንጭቼ እጠጣለሁ፤
11- በልቼ ስጨርስም አላህን አመሰግናለሁ።