መልስ-1 - ቀደም ብዬ እተኛለሁ፤
2 - የምተኛውም ጡሀራ ላይ ሆኘ ነው፤
3- በሆዴ ተደፍቼ አልተኛም፤
4 - ቀኝ እጄንም ከቀኝ ጉንጬ ስር አድርጌ በቀኝ ጎኔ እተኛለሁ፤
5- አልጋዬን አራግፋለሁ፤
6- አየተል-ኩርሲይን፣ ሱረቱል ኢኽላስን እና ከአል-ሙዓዊዘተይንን ሶስት ጊዜ ከቀራሁ በኋላ እንዲህ እላለሁ: 5- "ቢስሚከሏሁመ አሙቱ ወአሕያ" (ትርጉሙም: አላህ ሆይ! የምኖረውም የምሞተውም በስምህ ነው።)
7- ለፈጅር ሰላት እነቃለሁ፤
8- ከእንቅልፌ በነቃሁም ጊዜ እንዲህ እላለሁ:- "አልሐምዱ ሊላሂ አልለዚ አሕያና በዕደ ማ አማተና ወኢለይሂ ኑሹር" (ትርጉሙም: ምስጋና ከሞትን በኋላ ህያው ላደረገን አላህ የተገባ ነው። መመለሻ ወደርሱው ብቻ ነው።"