ጥ 11፡ የመኝታ ስርአትን (አዳብ) ጥቀስ?

መልስ-1 - ቀደም ብዬ እተኛለሁ፤

2 - የምተኛውም ጡሀራ ላይ ሆኘ ነው፤

3- በሆዴ ተደፍቼ አልተኛም፤

4 - ቀኝ እጄንም ከቀኝ ጉንጬ ስር አድርጌ በቀኝ ጎኔ እተኛለሁ፤

5- አልጋዬን አራግፋለሁ፤

6- አየተል-ኩርሲይን፣ ሱረቱል ኢኽላስን እና ከአል-ሙዓዊዘተይንን ሶስት ጊዜ ከቀራሁ በኋላ እንዲህ እላለሁ: 5- "ቢስሚከሏሁመ አሙቱ ወአሕያ" (ትርጉሙም: አላህ ሆይ! የምኖረውም የምሞተውም በስምህ ነው።)

7- ለፈጅር ሰላት እነቃለሁ፤

8- ከእንቅልፌ በነቃሁም ጊዜ እንዲህ እላለሁ:- "አልሐምዱ ሊላሂ አልለዚ አሕያና በዕደ ማ አማተና ወኢለይሂ ኑሹር" (ትርጉሙም: ምስጋና ከሞትን በኋላ ህያው ላደረገን አላህ የተገባ ነው። መመለሻ ወደርሱው ብቻ ነው።"