መልስ-1- በአብሮነት የተቀማመጡትን ሰዎች ሰላም እላለሁ፤
2 - በአብሮነት ከተቀማመጡት ሰዎች ጫፍ ላይ ባገኘሁት ክፍት ቦታ እቀመጣለሁ፤ ማንንም ከተቀመጠበት አላስነሳም፤ በሁለት ሰዎች መካከል የምቀመጠውም ከፈቀዱልኝ ብቻ ነው፤
3- አቀማመጤንም ሌላም ሰው ለመቀመጥ እንዲችል አድርጌ አሰፋለሁ፤
4- ተቀማማጮቹን በንግግራቸው መሀል አላቋርጣቸውም፤
5- ከተቀመጡት ሰዎች መካከል መሄድ ካለብኝም ከመሄዴ በፊት አስፈቅዳቸዋለሁ፤
6- አብሮ የመቀማመጣችን ጊዜው ካለቀም (የሚከተለውን) የመቀማመጥ ከፋራ ዱዓእ አደርጋለሁ: "ሱብሓነከሏሁመ ወቢሓምዲከ አሽሀዱ አን ላ ኢላሃ ኢላ አንተ አስተግፊሩከ ወአቱቡ ኢለይክ" (ትርጉሙም: ክብርና ምስጋና ላንተ ይሁን፤ ከአንተ በቀር ሌላ አምላክ እንደሌለም እመሰክራ ለሁ፤ መሀርታህንም እከጅላለሁ ወደ አንተም ተፀፅቻለሁ።)