ጥያቄ 9፡- “'ላ ሐውላ ወላ ቁወተን ኢላ ቢላህ' (ትርጉሙም: በአላህ ካልሆነ በቀር ምንም ሃይልም ሆነ ብልሀት የለም) ...” የሚለውን ሐዲሥ ሙላና ከሐዲሡ ከምናገኛቸው ቁምነገሮች መካከልም የተወሰኑትን ጥቀስ?

መልስ - ከአቢ ሙሳ ረዲየሏሁ ዓንሁ በተላለፈ ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ “'ላ ሐውላ ወላ ቁወተን ኢላ ቢላህ' (ትርጉሙም: በአላህ ካልሆነ በቀር ምንም ኃይልም ሆነ ብልሀት የለም) ማለት ከጀነት ድልቦች መካከል አንዱ ነው።" ቡኻሪይ እና ሙስሊም ዘግበውታል።

ከሐዲሡ ከሚወሰዱ ቁምነገሮች መካከል፡

1- የዚህ ቃል ትሩፋት እና ከጀነት ድልቦችም አንዱ ስለመሆኑ፤

2- የትኛውም ባርያ በሀይሉም ይሁን በብልሀት ብቻ ከመተማመን ተቆጥቦ በአላህ ብቻ መደገፍ እንደሚገባው፤

* አስረኛው ሐዲሥ፡