መልስ - ከአቢ ሙሳ ረዲየሏሁ ዓንሁ በተላለፈ ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ “'ላ ሐውላ ወላ ቁወተን ኢላ ቢላህ' (ትርጉሙም: በአላህ ካልሆነ በቀር ምንም ኃይልም ሆነ ብልሀት የለም) ማለት ከጀነት ድልቦች መካከል አንዱ ነው።" ቡኻሪይ እና ሙስሊም ዘግበውታል።
ከሐዲሡ ከሚወሰዱ ቁምነገሮች መካከል፡
1- የዚህ ቃል ትሩፋት እና ከጀነት ድልቦችም አንዱ ስለመሆኑ፤
2- የትኛውም ባርያ በሀይሉም ይሁን በብልሀት ብቻ ከመተማመን ተቆጥቦ በአላህ ብቻ መደገፍ እንደሚገባው፤
* አስረኛው ሐዲሥ፡