ጥያቄ 7፡- ‹‹ማናችሁም ቢሆን ለወንድሙ እስኪወድ ድረስ ...›› የሚለውን ሐዲሥ ሙላና ከሐዲሡ ከምናገኛቸው ቁምነገሮች መካከልም የተወሰኑትን ጥቀስ?

መልስ - ከአነስ ኢብኑ ማሊክ አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸው በተላለፈ ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ «ማናችሁም ቢሆን ለራሱ የሚወደውን ለወንድሙ እስካልወደደ ድረስ ኢማኑ አልተሟላም።" ቡኻሪይ እና ሙስሊም ዘግበውታል።

ከሐዲሡ ከሚወሰዱ ቁምነገሮች መካከል፡

1- ማንኛውም አማኝ ለራሱ የሚወደውን ለሌሎች አማኞችም መውደድ እንዳለበት፤

- ያን ማድረጉም ከኢማን ሙሉነት እንደሆነ

ስምንተኛው ሐዲሥ