ጥ 6፡ “እኔ እርሱ ዘንድ ይበልጥ የተወደድኩ እስካልሆንኩ ድረስ እምነቱ አልተሟላም...” የሚለውን ሐዲሥ ሙላና ከሐዲሡ ከምናገኛቸው ቁምነገሮች መካከል የተወሰኑትንም ጥቀስ?

መልስ - ከአነስ ኢብኑ ማሊክ አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸው በተላለፈ ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ «ከአባቱ፣ ከልጁ እና ከመላው የሰው ልጆችም ሁሉ እርሱ ዘንድ ይበልጥ ተወዳጅ የሆንኩት እኔ እስካልሆንኩለት ድረስ ማናችሁም ቢሆን አላመናችሁም።" ቡኻሪይ እና ሙስሊም ዘግበውታል።

ከሐዲሡ ከሚወሰዱ ቁምነገሮች መካከል፡

- ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ከሰዎች ሁሉ በላይ ይበልጥ ተወዳጅ መሆን እንዳለባቸው፤

- እርሳቸውን ከማንም በላይ መውደዱም ከኢማን ምሉእነት እንደሆነ፤

ሰባተኛው ሐዲሥ