ጥ 4፡- ‹‹ከሙእሚኖች መካከል ይበልጥ ኢማናቸው የተሟሉት...›› የሚለውን ሐዲሥ ሙላና ከሐዲሡ ከምናገኛቸው ቁምነገሮች የተወሰኑትንም ጥቀስ?

መልስ - ከአቡ ሁረይራ አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸው በተላለፈ ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ «ከሙእሚኖች መካከል ይበልጥ ኢማናቸው የተሟላው መልካም ሥነ-ምግባር ያላቸው ናቸው።» ቲርሚዚይ ዘግበውታል፤ ሐዲሡንም «ሐሰኑን ሰሒሕ" ብለውታል።

ከሐዲሡ የሚወሰዱ ቁምነገሮች፡

1- ለመልካም ስነምግባርን ማበረታታት (ማነሳሳት)

2- የስነምግባር መሟላት የኢማን መሟላት አካል መሆኑ፤

3- ኢማን የሚጨምርና የሚቀንስ መሆኑ፤

አምስተኛው ሐዲሥ፡