መልስ - ከአቡ ሁረይራ አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸው በተላለፈ ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ «ከሙእሚኖች መካከል ይበልጥ ኢማናቸው የተሟላው መልካም ሥነ-ምግባር ያላቸው ናቸው።» ቲርሚዚይ ዘግበውታል፤ ሐዲሡንም «ሐሰኑን ሰሒሕ" ብለውታል።
ከሐዲሡ የሚወሰዱ ቁምነገሮች፡
1- ለመልካም ስነምግባርን ማበረታታት (ማነሳሳት)፤
2- የስነምግባር መሟላት የኢማን መሟላት አካል መሆኑ፤
3- ኢማን የሚጨምርና የሚቀንስ መሆኑ፤
አምስተኛው ሐዲሥ፡