ጥያቄ 3፡ "ረሱል ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም ዘንድ ተቀምጠን ሳለ..." የሚለውን ሐዲሥ ሙላና ከሐዲሡ የምናገኛቸውን የተወሰኑ ቁምነገሮችንም ጥቀስ?

«ከእለታት አንድ ቀን የአላህ መልእክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ዘንድ ተቀምጠን ሳለን ልብሱ በጣም ነጭ ፀጉሩ በጣም ጥቁር የሆነ ሰው ብቅ አለ። የመንገደኛ ምልክትም አይታይበትም ከኛ መካከልም የሚያውቀው ሰው የለም። ወደ ነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ተጠግቶ ጉልበቱን ከጉልበታቸው አስደግፎ ተቀመጠ። እጁንም ታፋው ላይ አደረገና “አንተ ሙሐመድ ሆይ! እስኪ ስለ ኢስላም ንገረኝ?” አላቸው። የአላህ መልዕክተኛም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ” ኢስላም ማለት ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም ሙሐመድም የእርሱ መልዕክተኛ ናቸው ብለህ ልትመሰክር፣ ሶላት (ስርአቱን አሟልተህ) ልትሰግድ፣ ዘካን ልታወጣ፣ ረመዳንን ልትፆም፣ የጉዞውን ጣጣ ከቻልክ ደሞ ሐጅ ልታደርግ ነው።” አሉት። “እውነት ብለሃል” አላቸው። “ራሱ ጠይቆ ራሱ ‘ትክክል ነህ’ ይላቸዋል ብለን ተገረምን!”» (ከዚያም) «“ስለኢማን ንገረኝ እስኪ!” አላቸው። እርሳቸውም “በአላህ፣ በመላእክቶቹ፣ በመጽሐፍቶቹ፣ በመልእክተኞቹ፣ በመጨረሻው ቀን ልታምንና በቀደርም ክፉውም ሆነ ደጉን ልታምን ነው።” አሉት። “እውነት ብለሃል!” አላቸው። “እስኪ ደሞ ስለ ኢሕሳን ንገረኝ!” አላቸው። እርሳቸውም “አላህን ልክ እንደምታየው ሆነህ ልታመልከው ነው፤ አንተ ባታየውም እርሱ ያይሃልና።” “ስለ ሰዓቲቱስ ንገረኝ እስኪ!” አላቸው። እርሳቸውም “ተጠያቂው ከጠያቂው የተሻለ የሚያውቀው ነገር የለም።” አሉት። “ስለምልክቶቹ ንገረኝ!” አላቸው። እሳቸውም “ሴት ባርያ ጌታዋን (አለቃዋን) መውለዷ፣ ጫማና ልብስ የሌላቸው የሆኑ እረኞች በህንፃ ሲወዳደሩ ታያለህ” አሉትና ሄደ። ከዚያም ለተወሰነ ጊዜ ቆየን የአላህ መልዕክተኛም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ዑመር ሆይ! ጠያቂው ማን እንደነበር ታውቃለህ?” አሉኝ። እኔም “አላህና መልዕክተኛው ይበልጥ ያውቃሉ” አልኩኝ። እርሳቸውም “ጂብሪል ነው! የዲናችሁን ጉዳይ ሊያስተምራችሁ መጥቶ(ነው)።” አሉኝ። ሙስሊም ዘግበውታል።

ከሐዲሡ ከሚወሰዱ ቁምነገሮች መካከል፡

1- አምስቱ የእስልምና መሰረቶች ተወስተዋል። እነርሱም፦

“ላ ኢላሃ ኢለሏህ ሙሐመዱን ረሱሉሏህ” ብሎ በአሏህ ብቸኛ ተመላኪነትና በነብዩ ሙሐመድ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን የአሏህ መልዕክተኝነት መመስከር።

ሰላትን አሟልቶ መስገድ።

ዘካን መስጠት።

የረመዳንን ወር መፆም።

ወደ ተከበረው የአላህ ቤት ሂዶ ሐጅ ማድረግ።

2- የእምነት መሰረቶች ስድስት መሆናቸው። ስድስት ሲሆኑ እነርሱም፦

በአላህ ማመን።

በመላዕክቱ።

በመጽሐፍቱ።

በመልዕክተኞቹ።

በመጨረሻው ቀን እና

በክፉዉም በደጉም በቀደር ማመን ናቸው።

3- የኢሕሳን ምሰሶ ተወስቷል፤ እርሱም አንድ ምሰሶ ብቻ ያለው ሲሆን ይኸውም: አሏህን ልክ እንደምታየው ሆነህ ልታመልከው ነው። አንተ ባታየውም እርሱ ያይሀልና።

4- ዕለተ ትንሣኤ ጊዜው መች እንደሆነ የሚያውቀው የላቀው አላህ ብቻ መሆኑን (ተገልጿል)

አራተኛው ሐዲሥ፡