ጥያቄ 2፡- “በዚሁ ጉዳያችን አዲስ ፈሊጥ ያመጣ...” የሚለውን ሐዲሥ ሙላና ከሐዲሡ የምናገኛቸውን የተወሰኑ ቁምነገሮችንም ጥቀስ?

መልስ- ከምእመናን እናት ኡሙ ዐብደሏህ ዓኢሻ ረዲየሏሁ ዐንሁማ በተላለፈ ሐዲሥ እንዲህ ብላለች፦ "የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፡- "በዚሁ ጉዳያችን ከእርሱ ያልሆነን አዲስ ፈሊጥ ያመጣ ይዞት የመጣው ፈሊጥ ውድቅ ነው።" ቡኻሪይ እና ሙስሊም ዘግበውታል።

ከሐዲሡ ከሚወሰዱ ቁምነገሮች መካከል፡

1- በሃይማኖት ውስጥ አዲስ ፈጠራ ማምጣት የተከለከለ መሆኑ።

2- አዲስ መጤ ስራዎች ተቀባይነት የሌላቸው ውድቅ መሆናቸው።

* ሦስተኛው ሐዲሥ፡