ጥ 13፡ “ከአንድ ሰው እስልምና ማማሩ…” የሚለውን ሐዲሥ ሙላና ከሐዲሡ የምናገኛቸውን የተወሰኑ ጥቅሞቹንም ግለጽ?

መልስ - ከአቡ ሁረይራ አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸው በተላለፈ ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ “የአንድ ሰው እስልምናው ያማረ ለመሆኑ ምልክቱ ከማይመለከተው ነገር መታቀቡ ነው።" ቲርሚዚይና ሌሎችም ዘግበውታል።

ከሐዲሡ ከሚወሰዱ ቁምነገሮች መካከል፡

1- ማንኛውም ሰው ለዲኑም ለዱኒያውም የማይመለከተውን (የማይጠቅመውን) ነገር መተው እንዳለበት፤

2- እንቶፈንቶ መተው ከእስልምና ማማር እንደሆነ

* አስራ አራተኛው ሐዲሥ: