ጥ 11፡ “ከዱኒያ የመሰናበቻ ቃሉ 'ላ ኢላሃ ኢለሏህ' የሆነ ሰው...” የሚለውን ሐዲሥ ሙላና ከሐዲሡ ከምናገኛቸው ቁምነገሮች መካከልም የተወሰኑትን ጥቀስ?

መልስ - ከሙዓዝ ኢብኑ ጀበል ረዲየሏሁ ዓንሁ በተላለፈ ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ “ከዱኒያ የመሰናበቻ ቃሉ 'ላ ኢላሃ ኢለሏህ' የሆነ ሰው ጀነት ገባ።" አቡ ዳውድ ዘግበውታል።

ከሐዲሡ ከሚወሰዱ ቁምነገሮች መካከል፡

1- የ'ላ ኢላሃ ኢለሏህ' ትሩፋት፤ ማንኛውም ባርያ ጀነት የሚገባው በርሷው መሆኑ፤

2- ከዱኒያ የመሰናበቻ ቃሉ 'ላ ኢላሃ ኢለሏህ' የሆነ ሰው ያለው የላቀ ትሩፋት፤

* አስራ ሁለተኛው ሐዲሥ: