10፡- “አዋጅ! በሰውነት ውስጥ አንድ ቁራጭ ስጋ አለች…” የሚለውን ሐዲሥ ሙላና ከሐዲሡ ከምናገኛቸው ቁምነገሮች መካከልም የተወሰኑትን ጥቀስ?

መልስ - ከአን-ኑዕማን ቢን በሺር አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸው እንደተላለፈው የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ ብሏል፡- “አዋጅ! በሰውነት ውስጥ አንዳች ቁራጭ ስጋ አለች። ይህች ቁራጭ ስጋ ከተስተካከለች ሰውነት ሁሉ ይስተካከላል፤ እርሷ ከተበላሸች ደግሞ ሰውነት ሁሉ ይበላሻል።አዋጅ! እርሷም ልብ ነች።" ቡኻሪይ እና ሙስሊም ዘግበውታል።

ከሐዲሡ ከሚወሰዱ ቁምነገሮች መካከል፡

1- የልብ መስተካከል ውጭም ዉስጥም እንዲስተካከሉ ያደርጋል፤

2- ልብ እንዲስተካከል ትኩረት የመስጠት አስፈላጊነት፤ ምክንያቱም ሰውነት የሚስተካከለው በርሷው ነውና፤

* አስራ አንደኛው ሐዲሥ: