መልስ - ከአሚረል ሙእሚኒን አቡ ሐፍስ ዑመር ኢብኑል ኸጧብ ረዲየላሁ ዐንሁ በተላለፈ ሐዲሥ እንዲህ ብለዋል፡- "የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ፡- "የትኛውም ድርጊት ዋጋው ከጀርባ ባለመው እሳቤ (ኒያው) ላይ የተመሰረተ ነው። ማንኛውም ሰው የሚመነዳውም ባለመው ብቻ ነው። ለአላህና ለመልዕክተኛው ሲል የተሰደደ ሰው የተሰደደው ለአላህና ለመልእክተኛው (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሆኖለታል፤ የዱንያን ጥቅም ለማግኘት ወይም ሴትን ለማጨት ብሎ የተሰደደ ሰውም እንዲሁ መሰደዱ ለተሰደደለት ጉዳይ ነው።" ቡኻሪይ እና ሙስሊም ዘግበውታል።
ከሓዲሡ ከሚወሰዱ ቁምነገሮች መካከል፡
1- ማንኛውም አምልኮ ሰላትም ሆነ ፆም፣ ሐጅም ይሁን ሌሎች ተግባራት ሁሉ ኒያ ሊኖራቸው የግድ ነው።
2 - ለላቀው አላህ ብሎ የሚያከናውን ሁሉ ኢኽላሱን ለአሏህ ብቻ ሊያጠራ ይገባል።
* ሁለተኛው ሐዲሥ፡