መልስ- ሱረቱ ቁረይሽ እና ተፍሲሯ፦
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።
{ቁረይሾችን ለማላመድ(ባለዝሆኖቹን አጠፋ)። 1 * የብርድና የበጋን ወራት ጉዞ ሊያላምዳቸው ይህንን ሠራ። 2 * ስለዚህ የዚህን ቤት (የከዕባን) ጌታ ይግገዙ። 3 * ያንን ከረኃብ ያበላቸውን ከፍርሃትም ያረካቸውን (ጌታ ያምልኩ)። 4} (ሱረቱ ቁረይሽ፡ 1-4)።
ተፍሲር፡
1- {ቁረይሾችን ለማላመድ (ባለዝሆኖቹን አጠፋ)። 1} በክረምት እና በበጋ ወቅት የለመዱትን ጉዞ የተመለከተ ነው።
2- {የብርድና የበጋን ወራት ጉዞ ሊያላምዳቸው ይህንን ሠራ። 2} በክረምት ወደ የመን እና በበጋ ደግሞ ወደ ሻም የሚያደርጉት ጉዞ ነው።
3- {ስለዚህ የዚህን ቤት (የከዕባን) ጌታ ይግገዙ። 3} የዚህ የተቀደሰ ቤት ጌታ የሆነውን እና ይህንንም ጉዞ ያገራላቸውን አላህን በርሱም ምንንም ሳያጋሩ እርሱን ብቻ ያምልኩ።
4- {ያንን ከረኃብ ያበላቸውን ከፍርሃትም ያረካቸውን (ጌታ ያምልኩ)። 4} ያም በዓረቦች ልቦና ውስጥ ባሳፈነው የሐረምን እና የነዋሪዎቹን ክብር በማላቅ ከረሃብ መግቧቸው ከፍርሃትም ያዳናቸው ነው።