ጥ 6፡ ሱረቱ አል'ዐስርን ቅራና ተፍሲሩን ግለፅ?

መልስ - ሱረቱል ዐስር እና ተፍሲሯ፦

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።

{በጊዚያቱ እምላለሁ፤ 1 * ሰው ሁሉ በእርግጥ በከሳራ ውስጥ ነው። 2 * እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት፣ በእውነትም አደራ የተባባሉት፣ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ። 3} [ሱረቱል ዐስር: 1-3]

ተፍሲር፡

1- {በጊዚያቱ እምላለሁ፤ 1} ጥራት ይገባውና በጊዜያቱ ማለ።

2- {ሰው ሁሉ በእርግጥ በከሳራ ውስጥ ነው። 2} ማለትም፡- የሰው ልጆች ሁሉ በውድቀት እና በጥፋት ላይ ናቸው።

3- {እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት፣ በእውነትም አደራ የተባባሉት፣ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ። 3} እነዚያ አማኝ ሆነው መልካም ሥራዎችንም የሠሩት፤ ወደ እውነትም የተጣሩ በርሱም ላይ የታገሡት ከኪሳራ የዳኑ ናቸው።