ጥ 4፡ ሱረቱል ቃሪዓን ቅራና ተፍሲሩንም ግለፅ?

መልስ- ሱረቱ አል'ቃሪዓህ እና ተፍሲሩ:

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።

{ቆርቋሪይቱ (ጩኸት)፤ 1 * ምን አስደናቂ ቆርቋሪ ናት! 2 * ቆርቋሪይቱም ምን እንደሆነች ምን አሳወቀህ? 3 * ሰዎች እንደ ተበታተነ ቢራቢሮ (ወይም ኩብኩባ) በሚሆኑበት ቀን፤ 4 * ጋራዎችም እንደ ተነደፈ ሱፍ በሚሆኑበት (ቀን ልቦችን በድንጋጤ ትቆረቁራለች።) 5 * ሚዛኖቹ የከበዱለት ሰውማ፤ 6 * እርሱ በምትወደድ ኑሮ ውስጥ ይሆናል። 7 * ሚዛኖቹም የቀለሉበት ሰውማ፤ 8 * መኖሪያው ሃዊያህ ናት፤ 9 * እርሷም ምን እንደ ሆነች ምን አሳወቀህ? 10 * (እርሷ) በጣም ተኳሳ እሳት ናት።} [ሱረቱል አል'ቃሪዓህ 1-11]

ተፍሲር፡

1- {"{ቆርቋሪይቱ (ጩኸት)፤ 1"} ከአስፈሪነቷ አንፃር የሰዎችን ልብ የምታንኳኳ የሆነችው ሰዓት።

2- {"ምን አስደናቂ ቆርቋሪ ናት! 2"} ከአስፈሪነቷ አንፃር የሰዎችን ልብ የምታንኳኳ የሆነችው ሰዓት ምንድን ነች?!

3- {"ቆርቋሪይቱም ምን እንደሆነች ምን አሳወቀህ? 3"} መልእክተኛ ሆይ! ከአስፈሪነቷ አንፃር የሰዎችን ልብ የምታንኳኳ የሆነችው ሰዓት ምንነት ምን የምታውቀው አለ?! እርሷ`ማ የቂያም ቀን ነች።

4- {"ሰዎች እንደ ተበታተነ ቢራቢሮ (ወይም ኩብኩባ) በሚኾኑበት ቀን፤ 4"} ሰዎች ልባቸው በሚቆረቆርበት ቀን እዚህም እዚያም ተበታትነው እንደተበተነ ቢራቢሮ (ወይም ኩብኩባ) ይሆናሉ።

5- {"ጋራዎችም እንደ ተነደፈ ሱፍ በሚሆኑበት (ቀን ልቦችን በድንጋጤ ትቆረቁራለች።) 5"} ተራሮችም ከእንቅስቃሴያቸው ቀላልነት አንፃር እንደ ክፍት ሱፍ ይሆናሉ።

6- {"ሚዛኖቹ የከበዱለት ሰውማ፤ 6"} መልካም ስራው ከመጥፎ ስራው የሚበልጥ የሆነለት ሰው`ማ።

7- {"እርሱ በምትወደድ ኑሮ ውስጥ ይሆናል። 7"} ጀነት ውስጥ በተጎናፀፈው አጥጋቢ ህይወት ላይ ነው።

8- {"ሚዛኖቹም የቀለሉበት ሰውማ፤ 8"} መጥፎ ስራው ከመልካም ስራው የሚበልጥ የሆነበት ሰው`ማ።

9- {"መኖሪያው ሃዊያህ ናት፤ 9"} በእለተ ትንሳኤ መኖሪያ እና ማረፊያው ጀሀነም ነው።

10- {"እርሷም ምን እንደ ሆነች ምን አሳወቀህ? 10"} አንተ መልእክተኛ ሆይ! - ምን እንደሆነች ምን አሳወቀህ?!

11- {"(እርሷ) በጣም ተኳሳ እሳት ናት።"} እርሷ ትኩሳቷ የበረታ እሳት ነች።