መልስ- ሱረቱ አል'ዓዲያት እና ተፍሲሯ፡-
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።
{እያለከለኩ ሯጮች በሆኑት (ፈረሶች) እምላለሁ። 1 * (በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በሆኑትም፤ 2 * በማለዳ ወራሪዎች በሆኑትም፤ 3 * በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤ 4 * በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ። 5 * ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው። 6 * እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው። 7 * እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው። 8 * (ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤ 9 * በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚሆን)። 10 * ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው። 11} [ሱረቱ አል'ዓዲያት: 1-11]
ተፍሲር፡
1- {"እያለከለኩ ሯጮች በሆኑት (ፈረሶች) እምላለሁ። 1"} አላህ ከሩጫ ብዛት የሚያለከልኩት ድምጽ በሚሰማ በሆኑ ፈረሶች ማለ።
2- {"(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በሆኑትም፤ 2"} ቋጥኞችን በኋይለኛው በመምታታቸው ምክንያት በቋጥኙ ላይ ከሚያደርሱት ተጽእኖ አንፃር እሳትን በሚለኩሱ ፈረሶችም ማለ።
3- {"በማለዳ ወራሪዎች በሆኑትም፤ 3"} በማለዳው ጠላት ላይ የሚበረቱ በሆኑ ፈረሶችም ማለ።
4- {"በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤ 4"} በሩጫቸው አቧራ የሚቀሰቅሱ በሆኑትም ማለ።
5- {"በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ። 5"} ፈረሰኞቻቸውም በርካታ በሆኑ ጠላቶች መካከል የሚሰርጉባቸው በሆኑ ማለ።
"} ሰውም ጌታው ከርሱ የሚፈልገውን ደግ ነገር ከማድረግ ይነፍጋል።
"} መልካምን የሚከለክል መሆኑ ግልጽ በመሆኑ የማይክደው የሚመሰክረው ጉዳይ ነው።
8- {"እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው። 8
"} ለገንዘብም ድንበር ያለፈ ውዴታ ያለው በመሆኑም ንፉግ ነው።
9- {"(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤ 9"} ይህ በቅርቢቱ ሕይወት የተታለለ ሰው አላህ በመቃብር ውስጥ ያሉትን ሙታንን አስነስቶ ለመተሳሰብና ለፍርድም ከምድር በሚያስወጣቸው ጊዜ ነገሩ እንዳሰበው እንዳልሆነ አያውቅምን?!
10- {"በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚሆን)። 10"} ከሀሳብም ከእምነትም አኳያ በልቦች ውስጥ ያለውም ሌላውም ነገር ጎልቶና ግልፅ ሆኖ ይወጣል።
11- {"ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው። 11"} ጌታቸው በዚያ ቀን በነርሱ ላይ ዐዋቂ ነው። ከባሮቹ ምንም ነገር የማይደበቅበትና ለነርሱም በስራቸው ምንዳቸውን የሚከፍላቸው ነው።