ጥያቄ 3፡ ሱረቱ አል'ዓዲያትን ቅራና ተፍሲሩንም አስቀምጥ?

መልስ- ሱረቱ አል'ዓዲያት እና ተፍሲሯ፡-

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።

{እያለከለኩ ሯጮች በሆኑት (ፈረሶች) እምላለሁ። 1 * (በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በሆኑትም፤ 2 * በማለዳ ወራሪዎች በሆኑትም፤ 3 * በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤ 4 * በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ። 5 * ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው። 6 * እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው። 7 * እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው። 8 * (ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤ 9 * በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚሆን)። 10 * ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው። 11} [ሱረቱ አል'ዓዲያት: 1-11]

ተፍሲር፡

1- {"እያለከለኩ ሯጮች በሆኑት (ፈረሶች) እምላለሁ። 1"} አላህ ከሩጫ ብዛት የሚያለከልኩት ድምጽ በሚሰማ በሆኑ ፈረሶች ማለ።

2- {"(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በሆኑትም፤ 2"} ቋጥኞችን በኋይለኛው በመምታታቸው ምክንያት በቋጥኙ ላይ ከሚያደርሱት ተጽእኖ አንፃር እሳትን በሚለኩሱ ፈረሶችም ማለ።

3- {"በማለዳ ወራሪዎች በሆኑትም፤ 3"} በማለዳው ጠላት ላይ የሚበረቱ በሆኑ ፈረሶችም ማለ።

4- {"በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤ 4"} በሩጫቸው አቧራ የሚቀሰቅሱ በሆኑትም ማለ።

5- {"በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ። 5"} ፈረሰኞቻቸውም በርካታ በሆኑ ጠላቶች መካከል የሚሰርጉባቸው በሆኑ ማለ።

6- {"ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው። 6

"} ሰውም ጌታው ከርሱ የሚፈልገውን ደግ ነገር ከማድረግ ይነፍጋል።

7- {"እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው። 7

"} መልካምን የሚከለክል መሆኑ ግልጽ በመሆኑ የማይክደው የሚመሰክረው ጉዳይ ነው።

8- {"እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው። 8

"} ለገንዘብም ድንበር ያለፈ ውዴታ ያለው በመሆኑም ንፉግ ነው።

9- {"(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤ 9"} ይህ በቅርቢቱ ሕይወት የተታለለ ሰው አላህ በመቃብር ውስጥ ያሉትን ሙታንን አስነስቶ ለመተሳሰብና ለፍርድም ከምድር በሚያስወጣቸው ጊዜ ነገሩ እንዳሰበው እንዳልሆነ አያውቅምን?!

10- {"በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚሆን)። 10"} ከሀሳብም ከእምነትም አኳያ በልቦች ውስጥ ያለውም ሌላውም ነገር ጎልቶና ግልፅ ሆኖ ይወጣል።

11- {"ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው። 11"} ጌታቸው በዚያ ቀን በነርሱ ላይ ዐዋቂ ነው። ከባሮቹ ምንም ነገር የማይደበቅበትና ለነርሱም በስራቸው ምንዳቸውን የሚከፍላቸው ነው።