ጥ 14፡ ሱረቱል መሰድን ቅራ እና ተፍሲሯንም አስቀምጥ?

መልስ - ሱረቱል መሰድ እና ተፍሲሯ፦

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።

{የአቡ ለሀብ ሁለት እጆች ከሰሩ (ጠፉ፤ እርሱ) ከሰረም። 1 * ከእርሱ ገንዘቡና ያም ያፈራው ሁሉ ምንም አልጠቀመውም። 2 * የመንቀልቀል ባለቤት የሆነችን እሳት በእርግጥ ይገባል። 3 * ሚስቱም (ትገባለች)፤ እንጨት ተሸካሚ ስትሆን። 4 * በአንገትዋ ላይ ከጭረት የሆነ ገመድ ያለባት ስትሆን። 5} [ሱረቱ አል'መሰድ፡ 1-5]

ተፍሲር፡

1- {የአቡ ለሀብ ሁለት እጆች ከሰሩ (ጠፉ፤ እርሱ) ከሰረም። 1} የነብዩ ﷺ አጎት የሆነው አቡ ለሀብ ቢን ዐብዱል ሙጠሊብ ነብዩን ﷺ አዛ ሲያደርግ የነበረ በመሆኑ ስራው ኪሳራ ሆኖበት እጁ ከሰረ እንቅስቃሴውም ከንቱ ሆነ።

2- {ከእርሱ ገንዘቡና ያም ያፈራው ሁሉ ምንም አልጠቀመውም። 2} ገንዘቡ እና ልጁ እርሱን የጠቀሙት ምንድን ነው? ቅጣትን ከርሱ ሊያስቀሩለትም ሆነ እዝነትን ሊያመጡለት አልቻሉም።

3- {የመንቀልቀል ባለቤት የሆነችን እሳት በእርግጥ ይገባል። 3} በትንሳኤ ቀን ነበልባሏ አቃጣይ ወደ ሆነች እሳት ይገባታል።

4- {ሚስቱም (ትገባለች)፤ እንጨት ተሸካሚ ስትሆን። 4} ነብዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለምን በመንገዳቸው እሾህ እየጣለች የምታስቸግራቸው ሚስቱ ኡሙ ጀሚልም እንዲሁ ትገባታለች።

5- {በአንገትዋ ላይ ከጭረት የሆነ ገመድ ያለባት ስትሆን። 5} አንገቷ በተጠማዘዘ ገመድ ተቀፍድዳ ወደ ጀሀነም እሳት ትገባለች።