መልስ - ሱረቱል ካፊሩን እና ተፍሲሯ፦
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።
{በላቸው «እናንተ ከሓዲዎች ሆይ! 1 * ያንን የምትግገዙትን (ጣዖት አሁን) አልግገዛም። 2 * እናንተም እኔ የምግገዛውን (አምላክም አሁን) ተገዢዎች አይደላችሁም። 3 * እኔም ያንን የተገዛችሁትን (ወደፊት) ተገዢ አይደለሁም። 4 * እናንተም እኔ የምግገዛውን (አምላክም አሁን) ተገዢዎች አይደላችሁም። 5 * ለእናንተ ሃይማኖታችሁ አልላችሁ። ለእኔም ሃይማኖቴ አለኝ። 6} [ሱረቱል ካፊሩን፡ 1-6]
ተፍሲር፡
1- {በላቸው «እናንተ ከሓዲዎች ሆይ! 1} የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! እንዲህ በላቸው፡ እናንተ በአላህ የካዳችሁ ከሀድያን ሆይ!
2- {«ያንን የምትግገዙትን (ጣዖት አሁን) አልግገዛም። 2} እኔ አሁንም ይሁን ለወደፊት የምታመልኩትን ጣዖታት የማመልክ አይደለሁም።
3- {«እናንተም እኔ የምግገዛውን (አምላክም አሁን) ተገዢዎች አይደላችሁም። 3} እናንተም እኔ የማመልከውን ይሀውም አላህ በብቸኝነት አታመልኩም።
4- {«እኔም ያንን የተገዛችሁትን (ወደፊት) ተገዢ አይደለሁም። 4} እኔም እናንተ የምታመልኳቸውን ጣዖታት አላመልክም።
5- {«እናንተም እኔ የምግገዛውን (አምላክም አሁን) ተገዢዎች አይደላችሁም። 3} እናንተም እኔ የማመልከውን አላህ በብቸኝነት አታመልኩም።
6- {«ለእናንተ ሃይማኖታችሁ አልላችሁ። ለእኔም ሃይማኖቴ አለኝ። 6} እናንተም ለራሳችሁ የፈለሰፋችሁት መጤ ሃይማኖት አላችሁ፤ እኔም አላህ ወደኔ ያወረደልኝ ሃይማኖቴ አለኝ።