መልስ- ሱረቱ አል'ፋቲሓ እና ተፍሲሩ፡-
{"ቢስሚላሂ-ር-ሯሕማኒ-ር-ሯሒም" "በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።"(1) «አልሓምዱ ሊልላሂ ረቢል ዓለሚን» (ምስጋና ለዓለማት ጌታ ለአላህ የተገባው ነው) (2) "አር-ሯሕማኒ-ር-ሯሒም" "እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ ለሆነው።"(3) «ማሊኪ የውሚ‐ድ‐ዲን» (ትርጉሙም: የፍርዱ ቀን ባለቤት) (4) «ኢይ-ያከ ነዕቡዱ ወኢይያከ ነሰተዒን» (አንተን ብቻ እንገዛለን አንተንም ብቻ እርዳታን እንለምንሃለን) (5) «ኢህዲና‐ስ‐ሲሯጦል ሙስተቂም» (ትርጉሙም: ቀጥተኛውን መንገድ ምራን) (6) «ሲሯጦ‐ል‐ለዚነ አንዓምተ ዓለይሂም ቐይሪል መቕዱቢ ዓለይሂም ወለድዷሊን» (ትርጉሙም: የእነዚያ ፀጋህን የዋልክላቸውን ሰዎች መንገድ በነዚያ የተቆጣህባቸውን እና የተሳሳቱትንም አይደሉም። 7} [ሱረትይ አል'ፋቲሓ፡ 1 - 7]
ተፍሲር፡
ሱረቱል ፋቲሓ (የመክፈቻዋ ሱራ) የተባለችበት ምክንያት የአላህ ኪታብ የሚጀረው በእርሷ ስለሆነው ነው።
{"በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።"} ቁርኣንን መቅራቴን በአላህ ስም እጀምራለሁ፤ በላቀው አላህ እታገዝ ዘንድ ስሙን በማውሳት በረካውንም እንዳገኝ።
{አላህ} ማለት በእውነት የሚመለከው ብቸኛ ማለት ሲሆን ይህ ስያሜ ጥራት ይገባውና ከእርሱ ውጭ ማንም የሚጠራበት አይደለም።
{አር-ረሕማን} ማለትም ሁሉንም ያካለለ የሰፊ እዝነት ባለቤት ነው።
{አር-ረሒም} ማለትም ለምእመናኑ ልዩ እዝነት ያለው ነው።
2- {"ምስጋና ለዓለማት ጌታ ለአላህ የተገባው ነው"} ማለትም የውዳሴናም የፍፁምነትም ዓይነቶች ሁሉ ለአላህ ብቻ የተገባ ነው።
3- {"እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ ለሆነው።"} ማለትም ሁሉንም ነገር ያካለለ ሰፊ እዝነት ባለቤት እና ለምእመናን በልዩ ሁኔታ የሚደርስ የልዩ እዝነት ባለቤት ነው።
4- {"የፍርዱ ቀን ባለቤት"} ማለትም የምጽአት ቀን ባለቤቱ እርሱ ነው።
5- ("አንተን ብቻ እንገዛለን አንተንም ብቻ እርዳታን እንለምንሃለን") ማለትም ካንተ ውጭ ሌላን ሳናመልክ በብቸኝነት እናመክልሃለን ፤ አንተን ብቻ እገዛ እንጠይቅሃለን።
6- {"ቀጥተኛውን መንገድ ምራን"} ማለትም ለእስልምና እና ለሱና መገጠም ነው።
7- {"የእነዚያ ፀጋህን የዋልክላቸውን ሰዎች መንገድ በነዚያ የተቆጣህባቸውን እና የተሳሳቱትንም አይደሉም።"} ማለትም የክርስቲያኖችንና የአይሁዶችን መንገድ ሳይሆን የነብያትና የአላህ ደጋግ ባሮች መንገድ ምራን ማለት ነው።
ይህንን ከቀሩ በኋላ “አሚን” ማለቱ ሱና ነው። ማለትም የሚወደድ ነው።