ጥያቄ 21፡ ነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ከመካ ውጪ ያሉ ሰዎችን እንዴት ነበር ዳዕዋ ሲያደርጉላቸው የነበረው?

መልስ - ከመዲና የሆኑ አንሷሮች እሳቸው ዘንድ መጥተው በሳቸው አምነው በዳዕዋውም እንደሚተባበሯቸው ቃል እስኪገቡላቸው ድረስ ሰዎች የሚሰባሰቡባቸው በዓላትና አጋጣሚዎችን ጠብቀው ሰዎች ፊት እየቀረቡ ዳዕዋ ያደርጉ ነበር፤ የጧኢፍ ሰዎችንም ዳዕዋ ያደርጉላቸው ነበር።