መልስ- ሙሽሪኮች ምእመናንን ወደ አቢሲኒያ ነጉሥ እንዲሰደዱ እስኪፈቀድ ደረጃ ድረስ በእርሳቸውና በሙስሊሞች ላይ ግፋቸውን አጧጧፉት።
ሙሽሪኮች ነብዩን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ለመጉዳት እና ለመግደል በአንድ ድምፅ ተስማምተውም ነበር። ይሁን እንጅ አላህ እሳቸውን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ከሙሽሪኮቹ ለመታደግ አጎታቸው አቡጧሊብን ከለላ አደረገላቸው።