መልስ - የዉዱእ ሱናዎች የሚባሉት፡- ከሰሩት ተጨማሪ አጅር እና ምንዳን የሚያስገኝ ሲሆን ካልሰሩት ግን ወንጀል አይደለም ዉዱኡም ትክክል ነው።
1 - "ቢስሚላህ" ብሎ በአላህን ስም መጀመር
2- ሲዋክ መጠቀም (ጥርስን መፋቅ)
3 - የእጅ መዳፎችን ማጠብ
4- ጣቶችን ፈልፍሎ ማጠብ
5- የአካል ክፍሎችን ሲያጥቡ ሁለተኛና ሦስተኛ ጊዜ መድገም
6- በቀኝ መጀመር
7- ከዉዱእ በኋላ የሚከተለውን ዚክር ማለት፡- "አሽሀዱ አን ላኢላሃ ኢለሏህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ወአሽሀዱ አነ ሙሐመደን ዐብዱሁ ወረሱሉህ" ትርጉሙም: ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚገዙት አምላክ እንደሌለና ተጋሪ የሌለው ብቸኛ መሆኑን እመስክራለሁ፤ ሙሀመድም የአላህ መልዕክተኛው እና ባሪያው መሆናቸውንም እመስከራለሁ።
8- ከኋላው ሁለት ረከዓ መስገድ