መልስ - እነዚህ የትኛውም ሙስሊም ውዱእ ሲያደርግ አንዱንም ቢተው ያደረገው ውዱእ ትክክል የማይሆነለት ነው።
1- ፊትን መታጠብ መጉመጥመጥ እና አፍንጫን ጨምሮ ማጠብ ፤
2- እጅን እስከ ክርኖች ማጠብ፤
3- ጆሮን ጨምሮ ጭንቅላትን ማበስ፤
4- እግርን እስከ ቁርጭምጭሚት ድረስ ማጠብ፤
5- በውዱእ አካላት መካከል ያለውን ቅደም ተከተል መጠበቅ: ማለትም ፊትን ማጠብ፤ ከዚያም እጆችን ማጠብ፤ ከዚያም ጭንቅላትን ማበስና ከዚያም እግሮችን ማጠብ ነው።
6- ማከታተል፡- ማለትም ውዱእ ሲያደርጉ ከአንደኛው የውዱእ አካል ወደ ሌላኛው ሲሸጋገሩ አካላቱ እስኪደርቅ ድረስ ሳይዘገዩ ማከታተል ነው።
- ማለትም ግማሹን የዉዱእ አካላት አዳርሰው ዘግይቶ ከቆይታ በኋላ ወደሌላኛው አካል መሸጋገሩ ዉዱኡ ትክክለኛ እንዳይሆን ያደርገዋል።