ሐ- አላህን ማምለክን በማሰብ ጎህ ከሚቀድበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ጀንበር መጥለቅ ድረስ ጾምን ከሚያፈርሱ ነገሮች በመታቀብ አላህን ማምለክ ነው። ሁለት ዓይነትም ነው፦
የግዴታ ጾም፡- ከእስልምና ምሰሶዎች አንዱ የሆነውን የረመዷንን ወር መጾምን ይመስል።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {እናንተ ያመናችሁ ሆይ ጾም በነዚያ ከናንተ በፊት በነበሩት (ሕዝቦች) ላይ እንደ ተጻፈ በናንተም ላይ ተጻፈ (ተደነባ) ልትጠነቀቁ ይከጀላልና። 183} [ሱረቱል በቀራህ፡ 183]
ግዴታ ያልሆነ ጾም፡- በየሳምንቱ ሰኞ እና ሐሙስ መጾም እና ከየወሩ ሦስት ቀናትን መጾምን የመሳሰሉ ጾሞችን የሚመለከት ሲሆን ከእንዲህ ዓይነቶቹ በላጩ አያመል ቢድ የሚባሉት (በሒጅሪ አቆጣጠር የወሩን 13ኛ፣ 14ኛውና 15ኛውን) ቀናት መጾም ነው።