ጥ 3፡ የውዱእ ትሩፋቶችን ግለፅ?

መልስ - ነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "አንድ ሙስሊም ባሪያ" - ወይም "አማኝ የሆነ ሰው" - "ውዱእ በሚያደርግበት ጊዜ ፊቱን ሲያጥብ በዓይኑ የተመለከተው ኃጢአት ሁሉ ከፊቱ ከውኋው ጋር አብሮ ይፀዳለታል።” - ወይም “ከመጨረሻው የውሃ ጠብታ ጋር አብሮ ይራገፍለታል።” - “እጁን ሲታጠብም እንዲሁ እጆቹ እየዳሰሰች የፈፀመችው ኋጢአት ከውኋው ጋር አብሮ ይፀዳለታል።" - ወይም “ከመጨረሻው የውሃ ጠብታ ጋር አብሮ ይራገፍለታል።” - “እግሩን ሲታጠብም እንዲሁ እግሮቹ ስትራመድ የፈፀመችው ኋጢአት ከውኋው ጋር አብሮ ይፀዳለታል።" - ወይም “ከመጨረሻው የውሃ ጠብታ ጋር አብሮ ይራገፍለታል።” - “ልክ እንደዚሁ እያለ ከኃጢአት ንጹሕ እስኪሆነ ድረስ ይፀዳል።" ሙስሊም ዘግበውታል።