መልስ - ጁሙዓ ቀን ነው። ነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "ከቀኖቻችሁ በላጩ ጁምዓ ነው። በዚህ ቀን አደም ተፈጠረ፤ በዚህ ቀንም ሞተ፤ በዚህ ቀን ነው የመጨረሻው ቀንድ የሚነፋው፤ በዚህ ቀን ነው በድንጋጤ መሞት የሚከሰተው። በዚያ ቀን በኔ ላይ ሶለዋት አብዙ፤ ምክንያቱም ሶለዋታችሁ ለኔ ይቀርብልኛልና።" "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! አፈር በልቶዎት ሳለ ሰለዋታችን እንዴት ይቀርብሎታል?" አሏቸው፤ እርሳቸውም፦ "አላህ ምድርን የነቢያትን ሥጋ ከመብላት ከልክሏታል።" አቡ ዳውድና ሌሎችም ዘግበውታል።