መልስ - የሰላት ግዴታዎች እንደሚከተለው ስምንት ናቸው:
1- ከተክቢረተል ኢሕራም ውጭ ያሉ ተክቢራዎች፤
2- ኢማም ለሆነና ብቻውን ለሚሰግድ ሰው "ሰሚዐላሁ ሊመን ሓሚደህ" ማለቱ "ትርጉሙም፦ "አላህ የሚያመሰግኑትን ይሰማል" ነው፤
3 - "ረበና ወለከል ሓምድ" ይበል ትርጉሙም፡ “ጌታችን ሆይ! ምስጋና ላንተ ይሁን።” ነው፤
4 - «ሱብሓነ ረቢየል ዓዚም» ይበል ትርጉሙም፦ “ጥራት ይገባው ለታላቁ ጌታዬ" ነው፤
5 - «ሱብሓነ ረቢየል አዕላ» ይበል ትርጉሙም “ጥራት ይገባው ለላቀው ጌታዬ” ነው፤
6 - «ረቢ-ግ-ፊርሊ» ይበል ትርጉሙም “ጌታዬ ሆይ!ማረኝ” ነው፤
7- የመጀመሪያው ተሸሁድ፤
8- ለመጀመሪያው ተሸሁድ መቀመጥ፤