መልስ-1- ኹፉን የሚለብሰው ጠሃራ ሆኖ ማለትም ከውዱእ በኋላ መሆን አለበት።
2- ኹፎቹ ጠሃራ መሆን አለባቸው፤ ነጃሳ ላይ ማበስ አይፈቀድምና።
3- ኹፎቹ ውዱእ ሲደረግ መታጠብ ያለበትን ቦታ የሚሸፍኑ መሆን አለባቸው።
4- ማበሱ በተወሰነለት የጊዜ ገደብ ውስጥ መሆን አለበት፤ መንገደኛ ላልሆነ ነዋሪ፡ አንድ ቀን ከነሌሊቱ፤ መንገደኛ ደግሞ፡- ሶስት ቀናት ከነሌሊቱ ባለው ጊዜ ውስጥ ማበስ ይችላል።