ጥ 6፡ መሐመድ የአላህ መልእክተኛ መሆናቸውን መመስከር ማለት ምን ማለት ነው?

መልስ - ትርጉሙ፡- አላህ እሳቸውን አብሳሪና አስፈራሪ አድርጎ ለዓለማት የላካቸው መልዕክተኛው መሆናቸውን መመስከር ማለት ነው።

በዚህ ያመነ የሚከተሉት ነገሮች ግዴታ ይሆኑበታል፦

1- ያዘዙትን መታዘዝ፤

2- የተናገሩትን አምኖ መቀበል፤

3- እርሳቸውን አለማመፅ፤

4- እሳቸው በደነገጉት ካልሆነ በቀር አላህ አለማምለክ ነው። ይኸውም ሱናቸውን በመከተል እና ቢድዓን በመተው ነው።

የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ {መልክተኛውን የሚታዘዝ ሰው በእርግጥ አላህን ታዘዘ።} (ሱረቱ-አንኒሳእ፡ 80) ጥራት የተገባው አላህ እንዲህም ብሏል፦ {ከልብ ወለድም አይናገርም። እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም። 4} [ሱረቱ-ነጅም 3፡4] ልዕለ ኃያሉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ለእናንተ አላህንና የመጨረሻውን ቀን የሚከጅል ለሆነ ሰው፣ አላህንም በብዙ ለሚያወሳ በአላህ መልዕክተኛ መልካም መከተል አልላችሁ።21} [ሱረቱል አሕዛብ፡ 21]