ሐ - አላህ ሰማይ ላይ ከዓርሹ ከፍ ብሎ ከፍጡራን ሁሉ በላይ ነው ያለው። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ {(እርሱ) አልረሕማን ነው በዐርሹ ላይ (ለሱ ክብር በሚስማማ መልኩ) ከፍ አለ።} [ሱረቱ ጠሃ፡5] እንዲህም ብሏል፦ {እርሱም ከባሮቹ በላይ ሲሆን አሸናፊ ነው። እርሱም ጥበበኛው ውስጥ ዐዋቂው ነው። 18} [ሱረቱል አል-አንዓም፡ 18]