መልስ - ኢማን አላህን በመታዘዝ የሚጨምር እና አላህንም በማመፅ የሚቀንስ ነገር ነው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ፍጹም ምእምናን እነዚያ አላህ በተወሳ ጊዜ ልቦቻቸው የሚፈሩት፣ በነሱም ላይ አንቀጾቻችን በተነበቡ ጊዜ እምነትን የሚጨምሩላቸው፣ በጌታቸውም ላይ ብቻ የሚመኩት ናቸው። 2} [ሱረቱል አንፋል፡ 2]