ጥ33፡ እነዚህን ስሞች አብራራ?

መልስ- አላህ፡- ትርጉሙም ተጋሪ የሌለው ብቸኛው በእውነት የሚመለክ አምላክ ማለት ነው።

አር-ረብ፡- ትርጉሙም ጥራት የተገባው አምላካችን አላህ ብቸኛው የሁሉም ፈጣሪ፣ ባለቤት፣ ሰጪና አስተናባሪው ማለት ነው።

አስ-ሰሚዕ፡- የመስማት ችሎታው ሁሉንም ነገር የሚያካልል እና በዓይነትም በብዛት የተለያዩ የሆኑ ድምፆችን በሙሉ የሚሰማ ማለት ነው።

አል-በሲር፡ ሁሉንም ነገር የሚያይ እና ትንሹም ይሁን ትልቁን ሁሉ የሚመለከት ነው።

አል-ዓሊም፡ እውቀቱ ያለፈውን፣ የአሁኑንና የወደፊቱን ሁሉ ያካለለ ነው።

አር-ረሕማን፡ እዝነቱ ለእያንዳንዱ ህያው ፍጡር ሁሉ የተዘረጋ ሲሆን ፍጡራን ሁሉ በእዝነቱ ስር ናቸው።

አር-ረዛቅ፡- የሰውም፣ የጂንም እና የተንቀሳቃሽ ህያው ሁሉ ሲሳይ እርሱ ዘንድ የሆነ ነው።

አል-ሓይ፡- የማይሞት ህያው የሆነ ነው። ፍጥረታት ሁሉ ሟች ናቸው።

አል-ዓዚም፡ በስሙም በባህሪያቱም እንዲሁም በድርጊቶቹም ፍጹምነት እና ልዕልና ያለው ነው።