መልስ-
1- ከባዱ ኒፋቅ፡- ላይ ላዩን አማኝ መስሎ ክህደትን በውስጥ መደበቅ ነው።
ከእስልምና የሚያስወጣ ሲሆን ከከባዱ የክህደት ዓይነትም ነው።
የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {መናፍቃን በእርግጥ ከእሳት በታችኛው አዘቅት ውስጥ ናቸው። ለእነሱም ረዳትን አታገኝላቸውም። 145} [ሱረቱ አንኒሳእ፡ 145]
2 - መለስተኛ ሙናፊቅነት:
እንደ መዋሸት፣ ቃል ኪዳንን ማፍረስ እና እምነት መክዳት ያሉት ናቸው።
ከእስልምና የሚያስወጣ ባይሆንም ባለቤቱን ለቅጣት የሚዳርግ ኃጢአት ነው።
የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "የሙናፊቅ ምልክቱ ሶስት ነው፤ ሲናገር ይዋሻል፣ ቃል ሲገባ ቃሉን ያፈርሳል፣ ሲታመን ይክዳል።" ቡኻሪይ እና ሙስሊም ዘግበውታል።