ጥ 21፡ ክህደት በንግግር፣ በተግባር እና በእምነት የሚገለፅ ነው፤ ለእነዚህ ምሳሌ የሚሆኑትን ግለጽ?

መልስ - በንግግር ለምሳሌ፡ ጥራት የተገባው አላህን ወይንም መልዕክተኛው የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንን መስደብ።

በተግባር ለምሳሌ፡- ቁርኣንን በተግባር ማቃለል ወይም ከአላህ ውጭ ላለ አካል መስገድን።

በእምነት ለምሳሌ፡- ከኃያሉ አምላክ ሌላ ሊመለክ የሚገባው አካል እንዳለ ወይም ጥራት ይገባውና ከላቀው አምላካችን አላህ ጋ ሌላ አምላክ እንዳለ ማመንን።