ጥ 19፡ የወላእ (ለኢስላም ሲባል የሚደረግ ወዳጅነት) እና የበራእ (ለኢስላም ሲባል የሚደረግ ጠላትነት) እምነትን አብራራ?

መልስ- ወላእ ሲባል፡- ምእመናንን መወዳጀትና መደገፍ ነው።

የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {ምእምንና ምእምናትም ከፊሎቻቸው ለከፊሉ ረዳቶች ናቸው።} [ሱረቱ አትተውባህ፡ 71]

አል በራእ ሲባል ደግሞ፡ ከሓዲያንን የኢስላም ጠላትነታቸውን አውቆ ጠላት አድርጎ መያዝ ነው።

የላቀዉ አላህ እንዲህ ብሏል፦ {በኢብራሂምና በእነዚያ ከእርሱ ጋር በነበሩት (ምእምናን) መልካም መከተል አለቻችሁ። ለሕዝቦቻቸው «እኛ ከእናንተ ከአላህ ሌላ ከምትግገዘትም ንጹሖች ነን። በእናንተ ካድን። በአላህ አንድ ብቻ ሲኾን እስከምታምኑ ድረስ በእኛና በእናንተ መካከል ጠብና ጥላቻ ዘወትር ተገለጸ።» ባለ ጊዜ (መልካም መከተል አለቻችሁ)።} [ሱረቱል ሙምተሒናህ፡ 4]